Mamo Esmelealem Mihretu, Biography

Mamo E. Mihretu is the 10th Governor of the National Bank of Ethiopia (NBE). Before he was appointed as the Governor of NBE, Mr. Mamo served as the founding CEO of the Ethiopian Investment Holdings (EIH), the strategic investment arm of the government of Ethiopia. EIH manages all key commercial companies of the government of Ethiopia, such as Ethiopian Airlines and EthioTelecom.

Mr. Mamo is a member of Ethiopia’s Macroeconomic Council, which is the body that steers economic policy and strategic decisions. He has been a member and a Secretary of the Council for the last four and half years. He was an active member of the economic team that conceptualized, developed and implemented Ethiopia’s economic reform program.

As a Board member of the Commercial Bank of Ethiopia (CBE) for four years, the largest financial institution in the country, Mr. Mamo chaired CBE’s transformation program.

Mr. Mamo also served as a Senior Policy Advisor to the Prime Minister of Ethiopia and Ethiopia’s Chief Trade Negotiator from 2018-2021.While working at the Office of the Prime Minister, Mr. Mamo helped  create the policy and performance department that oversees performance outcomes of government agencies. Before joining the Ethiopian government in 2018. Mr. Mamo was a Senior Project Manager at the World Bank Group in Kenya from 2010 to 2018, working mainly on finance and competitiveness issues. Mr. Mamo obtained a Master’s Degree in Leadership, Public Administration and Economic Development from the Kennedy School of Government of Harvard University in the United States. He also holds a post-graduate degree in Trade and Investment from the Universities of Pretoria and University of Amsterdam. He was a gold medalist when he graduated from Addis Ababa University, School of Law.

 

የባንኩ ሴት ሠራተኞች ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ

የባንኩ ሴት ሠራተኞች ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሴት ሠራተኞች የዘንድሮውን የዓለም የሴቶች ቀን በድምቀት አከበሩ። ቀኑ “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በአገርአቀፍ ደረጃ ለ47ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል።

የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በባንኩ አዳራሽ የተከናወነውን ሥነሥርዓት በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የኮርፖሬት ሰርቪስ ም/ገዥ አቶ እዮብ ገብረኢየሱስ ዕለቱ ተከብሮ የሚውለው ለሴቶች የማይመቹ ሁኔታዎችን ማስወገድና በተለያየ መልክ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን መታገል እንደሚገባ ለማስገንዘብ መሆኑን ገልጸዋል።

በርግጥም “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚለው መሪ መልዕክት መሠረት ሁላችንም ጭቆናና ጥቃቶችን ልንታገላቸው ይገባል ብለዋል።

በተቋም ደረጃ ለሴቶች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር፣ አቅማቸውን ማሳደግና ወደ ሥልጣን ማምጣት የባንኩ አመራር የሚረዳው ጉዳይ ነው ያሉት ም/ገዢው፣ ሴቶችም በበኩላቸው ለዚህ አስተዋፅኦ ማድረግና ዝግጁ ሆኖ መገኘት እንደሚኖርባቸው አመልክተዋል።

የባንኩ የሴቶችና ወጣቶች ጉዳይ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት ወይዘሮ አምባወርቅ መኮንን ዕለቱን አስመልክቶ በሠጡት ገለጻ የሴቶችን ጉዳይ በሁለንተናዊ መልኩ ለመድረስ የማያቋርጥ ትግል እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።

ዕለቱ በአገራችን ለ47ኛ፣ በዓለምአቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ112ኛ ጊዜ ቢከበርም፣ አሁንም በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት አልቀረም፤ ሴቶችን ማጎናጸፍ የሚገባው ድል ገና በሚገባ ማሳካት አልተቻለም ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዕለቱን አስመልክቶ ቀደም ካሉት ዓመታት ጀምሮ ያደካሄዳቸውን መርሐግብሮች ያስታወሱት ወይዘሮ አምባወርቅ፣ በተጓዳኝም የባንኩን ሴት ሠራተኞች ከቁጥር፣ ከትምህርት ዝግጅትና አመራር ላይ ካላቸው ተሳትፎ አኳያ በአሀዝ በተደገፈ መረጃ ማብራሪያ ሠጥተዋል።

በመርሐግብሩ መሠረት ከባንኮች ክሊኒክ የመጡ ዶክተሮች በማህጸን ጫፍ ካንሰርና በጡት ካንሰር ላይ ትምህርታዊ ገለጻ የሠጡ ሲሆን፣ ከኦፕሪፍስ መጠለያ ማዕከል በመጡ ሕጻናት ኪናዊ ዝግጅት ቀርቧል፤ የዳቦ ቆረሳና ቡና የማፍላት ሥነሥርዓትም ተካሂዷል።

የኦፕሪፍስ ማዕከል ሀላፊ ወይዘሮ እንግዳወርቅ ታደሰ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል በህዳር 2015 ዓ.ም በማዕከሉ ተገኝቶ ያደረገውን ጉብኝትና ድጋፍ አስታውሰው፣ በቀጣይም ባንኩ ለማዕከሉ የሚያደርገው ድጋፍ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ሁሉም ወላጅ ልጆቹን (ሴቶችንም ሆነ ወንድ ልጆቹን) በቤትም ሆነ በውጭ፣ እንዲሁም ከቅርብ ዘመድም ጭምር መጠበቅ እንዳለበት ማዕከሉ የሚንከባከባቸው የጥቃት ሰለባ ሕጻናት መልክዕት መሆኑን ወይዘሮ እንግዳወርቅ አሳስበዋል። ምክንያቱም አብዛኞቹ ጥቃቶች ከሩቅ ሳይሆን ከቅርብ በተለይም “የእኔ” ከሚሉት ወገን የሚመጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የለውጥ ማኔጅመንት፣ ዕቅድና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አባተ ምትኩ እንዳሉት፣ “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ” የሚለውን መሪ ቃል ሁሉም ከልቡ ተግባራዊ ማድረግ አለበት።

በተቋም ደረጃ ሴት ሠራተኞችን በአቅም ግንባታ ከማሳደግና ወደ አመራር ሠጪነት እንዲበቁ ከማድረግ ጎን ለጎን ባንኩን ለሴቶች አመቺ የሥራ ቦታ እንዲሆንላቸው ሁሉንም አስቻይ ነገሮች ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

የሕጻናት ማቆያ (day care) ማዕከሉን ግንባታና ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቅቆ በፍጥነት ሥራ ላይ ማዋል የሚያስፈልግ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አባተ፣ ይህም የባንኩ ሴት ሠራተኞች ሥራቸውን በተረጋጋና በውጤታማነት እንዲያከናውኑ ለማስቻል በእጅጉ የሚያግዝ መሆኑን አብራርተዋል።

በተጨማሪም ነፍሰጡር እናቶች በመንግሥት የተሠጣቸው የወሊድ ፈቃድ አጠቃቀም ላይ በራሳቸው በነፍሰጡሮቹ ፍላጎት መሠረት ተመቻችቶ ተግባራዊ ቢደረግ መልካም መሆኑን አቶ አባተ ጠቁመዋል።

በዓመት አንድ ጊዜ በሚከበረው በሴት የሴቶች ቀን ላይ የባንኩ መካከለኛና ከፍተኛ ሴት አመራር አባላት እንደሚጠበቀው አለመሳተፋቸውን እንደክፍተት አንስተውታል።           አቶ አባተ በየዓመቱ መጠነኛም ቢሆን ለተለያዩ ግብረሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ እየሠጠንና ደማቅ በሆነ ሁኔታ እንድናከብር ለሚፈቅድልን የባንኩን የበላይ አመራር፣ እንዲሁም ጥሪያችንን አክብረው በበዓሉ ላይ ለሚታደሙ ሠራተኞች፣ በማህጸን ጫፍ ካንሰርና በጡት ካንሰር ላይ ትምህርታዊ ገለጻ ለሰጡት ዶክተሮች በመጨረሻም ለኦፕሪፍስ ማዕከል ምሥጋና አቅርበዋል።

የባንኩ ሠራተኞች 127ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ

የባንኩ ሠራተኞች 127ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት 127ኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት አከበሩ።

የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በባንኩ አዳራሽ በተከናወነው ሥነሥርዓት ላይ የማኔጅመንት አባላትና የባንኩ ሠራተኞች፣ የተገኙ ሲሆን፣ በልዩ ልዩ ሁነቶች መርሐግብሩ ተከናውኗል።

መርሐግብሩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የኮርፖሬት ሰርቪስ ም/ገዥ አቶ እዮብ ገብረኢየሱስ የአድዋ ድል ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን ብሎም ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት ተምሳሌት መሆኑን ገልጸዋል።

የአድዋ ድል ጥቁር ሕዝብም አሸናፊ እንደሆነ ለነጮቹም ሆነ ለመላው ዓለም ትምህርት የሠጠ መሆኑንና ለጸረ-ኮሎኒያሊዝም ትግል መነሻ ሊሆን እንደቻለ ታላላቅ ምሁራንና የአገራት መሪዎች ያረጋገጡት ጉዳይ መሆኑንንም አቶ እዮብ  አብነት ጠቅሰው አስረድተዋል።

ም/ገዢው እንዳስረዱት ከኔልሰን ማንዴላ ቀጥሎ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት ታቦ ምቤኪ በአንድ ወቅት ባደረጉት ገለጻ የአድዋ ድል ለነጮች የሚያስደነግጥ ትምህርት የሠጠ፤ ለተቀረው የዓለም ሕዝብ የነፃነት ፋና ወጊ መሆን የቻለ ትልቅ የታሪክ ክስተት መሆኑን አስረድተዋል።

“በመሆኑም የዘንድሮውን 127ኛ የአድዋ ድል በዓል ስናከብር አባቶቻችን ምን ያህል አኩሪ ታሪክ ሠርተው ያለፉ መሆኑን የምናስታውስበትና እኛም በአንድነት፣ በጀግንነትና በጽናት ታሪክ መሥራት የሚጠበቅብን መሆኑን ያስረዳል” ሲሉ አቶ እዮብ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የለውጥ ማኔጅመንት፣ ዕቅድና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አባተ ምትኩ አድዋን በተመለከተ ባቀረቡት አጭር ገለጻ፣ አድዋ በአባቶቻችን ከፍተኛ ተጋድልዎ የተደረገበትና በሚያስደንቅ ጀግንነት ድል የተገኘበት ጦርነት መሆኑን አስረድተዋል።

አቶ አባተ በገለጻቸው ስለ ጠርነቱ መንስዔ፣ ስለጣሊያኖች ዝግጅት፣ በአፄ ምኒልክ ስለተደረገው ጥሪ፣  እቴጌ ጣይቱ ለጣሊያን መንግሥት ስላስተላለፉት መልዕክት፣ ስለሃይል አሰላለፍ በመጨረሻም ስለተካሄደው ጦርነትና አባቶቻችን ስለተጎናጸፉት ድል አብራርተዋል።

በመርሐግብሩ በኢትዮጵያ ሴት ደራሲያን ማህበር አማካኝነት ኪናዊ ዝግጅት የቀረበ ሲሆን፣ የዳቦ ቆረሳ፣ ቡና የማፍላት ሥነሥርዓት መካሄዱ ለዝግጅቱ ድምቀት ሆኗል።

በመርሐግብሩ ማጠናቀቂያ ላይ አድዋን በተመለከተ የጥያቄና መልስ ውድድር የተካሄደ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ም/ገዥና ዋና ኢኮኖሚስት ለተወዳዳሪዎች የተዘጋጀውን ሥጦታ ሸልመዋል።

ም/ገዢው አቶ ፍቃዱ ድጋፌ በመጨረሻ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያውያን በየትኛውም ጊዜ በአገር ላይ የሚመጡ የውጭ ጥቃቶችን ለመቀልበስ በአንድነት የሚነሱ መሆናቸውን የአድዋ ድል ትክክለኛ ማሳያ መሆኑን አመልክተዋል። በመሆኑም በአድዋ ጦርነት ወቅት በአባቶቻችን ዘንድ የታየውን አንድነት፣ ጀግንነትና ጽናት አሁን ደግሞ እኛ ድህነትን ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት ላይ መረባረብ እንዳለብን ምክትል ገዥው አሳስበዋል።

“የተረጋጋ የውጭ ምንዛሬና ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት እንዲኖር ይሠራል”

የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ ገዥ
ኤልያስ ሳላህ

የተረጋጋ ዋጋና የውጭ ምንዛሬ እንዲሁም ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት የማክሮኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት በመሆናቸው የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ እነርሱ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አዲሱ የባንኩ ገዥ አቶ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ ገለጹ፡፡ ከፋይናንስ ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ጋርም በዘርፍ የ 6 ወር አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ጥር 24 ቀን 2015 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲሱ ህንፃ ዋናው አዳራሽ በተካሄደው ውይይት ላይ አቶ ማሞ የፋይናንስ ዘርፉ ብቻውን የቆመ ሳይሆን ከማክሮኢኮኖሚ ጋር ተያይዞ የሚጓዝ መሆን እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ በዚህ ዓመት በ 7 ነጥብ 5 በመቶ ያድጋል ተብሎ ለሚጠበቀው የአገሪቱ ኢኮኖሚ የፋይናንስ ሴክተሩ የራሱ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል፡፡ የባንኩ ዋነኛ ተልዕኮዎች የሆኑትን ዋጋ የማረጋጋትና የውጭ ምንዛሬ ተመን የማስፈን እንዲሁም ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት የመፍጠር ጥረት በቀጣይ የባንኩ ዋነኛ ትኩረቶች እንደሚሆኑ የጠቆሙት አቶ ማሞ፣ በቀጣይም የዋጋ ንረትን እንዳያባብስ በገንዘብ ፖሊሲው አማካኝነት የተጠና ሥራ እንደሚሠራም አስታውቀዋል፡፡ የፋይናንስ ዘርፉ በአጠቃላይ፣ በተለይም የባንክ ዘርፉ በአገር ዕድገት ላይ እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ ያነሱት ዋና ገዥው፣ ለአብነትም ባለፉት ስድስት ወራት ከ157 ቢሊዮን ብር በላይ የግምጃ ቤት ሰነድ መግዛቱን አመልክተዋል። ይህም የበጀት ጉድለትን በመሙላት ረገድ የፋይናንስ ዘርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ ያለው አስተዋጽኦ እየጨመረ መሆኑን እንደሚያሳይ የጠቆሙት አቶ ማሞ፤ ባንኮች የሚሰበስቡት የተቀማጭ ገንዘብ፣ ሃብትና የሚሰጡት ብድር በየዓመቱ በአማካይ በ30 በመቶ እያደገ ስለመሆኑም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ከባንክ ውጭ ያለው ገንዘብ ከ189 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ጠቁመው ይህም ለባንኮች ተጨማሪ ሃብት ለማሰባሰብ እድል የሚፈጥር እንደሆነ አመልክተዋል፡፡

የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የቦርድ አባላት ሥራ ጀመሩ

    • ይናገር ደሴ (/) የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሹመዋል

 

በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አህመድ የተሾሙት የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የቦርድ አመራር አባላት ሥራ ጀመሩ።

በቅርቡ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይጠበቅ የነበረውን የካፒታል ገበያ ባለሥልጣንን የሚያገለግሉ ስድስት የቦርድ አባላት ኅዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም. መሾማቸው ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) የቦርዱ ሰብሳቢ ሆነው ተሹመዋል።

ሌሎቹ የቦርዱ አባላት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድምአገኝ ነገራ፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ፣ ከተመድ የካፒታል ዴቨሎፕመንት ኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤት ደግሞ (ዶ/ር)ኢዮብ ተስፋዬ ፣የሒሳብና የኦዲት ቦርድ ዋና ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሒክመት አብደላ፣ የሴሬብሩስ ፍሮንቲየርስ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ኃይለ ሚካኤል እና የአዲስ አበባ ዩነቪርሲቲ መምህር አቶ አባተ አበበ ናቸው፡፡

ከኅዳር 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ የባለሥልጣኑ የቦርድ አባል ሆነው እንዲሠሩ የተመደቡት እነዚህ የቦርድ አባላት ማክሰኞ ኅዳር 27 ቀን 2015 የመጀመሪያ ስብሰባቸውን አካሂደው ሥራቸውን ጀምረዋል።

እነዚህ ተሿሚዎች በቦርድ አባልነት የተሰየሙት በካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1248 /2013 መሠረት ሲሆን፣ በአዋጁ መሠረት የቦርድ አባላቱ የሥራ ዘመን አምስት ዓመት እንደሆነ ተደንግጓል፡፡

በአዋጁ መሠረት የካፒታል ገበያ ማቋቋም ያስፈለገው ካፒታል በማሰባሰብ፣ የገንዘብ ሥርዓቱን በአዲዲስ ፈጠራዎች በመደገፍ እና የኢንቨስትመንት ስጋቶችን የመጋራት አሠራርን በማስፋፋት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ልማት ለመደገፍ እንዲቻል ነው። በተጨማሪም በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ  የሚፈጠሩ መዋቅራዊ ስጋቶችን ለመለየት፣ ለመከላከልና  ለመቀነስ በካፒታል ገበያ ላይ ጠንካራ የቅርብ ክትትልና የቅኝት ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በማስፈለጉ መሆኑን በአዋጁ ተደንግጓል።

 

The National Bank of Ethiopia was established in 1963 by proclamation 206 of 1963 and began operation in January 1964.

P.O.Box: 5550
Tel: +251 115 517 430
E-mail: nbeinfo@nbe.gov.et
Fax: +251 115 514 588
Avenue: Sudan Street

Navigation

Follow Us